ምዕራፍ 2 የህዝብ ተደራሽነት የዳሰሳ ጥናት (Amharic)
ይህ የዳሰሳ ጥናት የAurora ከተማ የተደራሽነት ጉዳዮችን (ተቋማት፣ አገልግሎቶች እና ፕሮግራሞች) እንዲሁም የከተማውን ተቋማት ለሚጠቀሙ አካል ጉዳተኞች የሚመለከቱ ልዩ ስጋቶችን ወይም ወሳኝ ቦታዎችን ለመለየት ይረዳል። ከተማው ከአሜሪካውያን የአካል ጉዳተኞች ሕግ (Americans with Disabilities Act, ADA) ጋር በተጣጣመ መልኩ እንቅፋቶችን ለማስወገድ የሽግግር ዕቅድ እያዘጋጀ ነው። ይህም የአደጋ ጊዜ ዝግጁነትን፣ ፓርኮችን እና የመዝናኛ ተቋማትን፣ እንዲሁም ሌሎች የከተማው ተቋማትን ያካትታል። የጥናቱ ጥረቶች ወዲያውኑ ማሻሻያዎችን ላያስከትሉ ቢችሉም፣ የሚዘጋጀው ዕቅድ ገንዘቡ እስከሚፈቅደው ድረስ ከተደራሽነት ጋር የተያያዙ ማስተካከያዎችን ለማድረግ ለከተማው ግልጽ አቅጣጫ እና የመንገድ ካርታ ይሰጣል።
የADA የሽግግር ዕቅድ ዝግጅት ከተማው አሁን ያሉ የስጋት ቦታዎችን ወይም ሊሻሻሉ የሚችሉ አካባቢዎችን ለመለየት የሚረዳ መረጃ ለማግኘት ተስፋ የሚያደርግበትን የህዝብ ተሳትፎ ፕሮግራም ያካትታል። ይህ የዳሰሳ ጥናት በወረቀት ቅጂ፣ በትልቅ የፊደል መጠን ወይም በኦዲዮ ቅርፀት ሊቀርብ ይችላል። ይህን የዳሰሳ ጥናት በአማራጭ ቅርጸት ለመቀበል፣ እባክዎ በ 303.326.8858 ወይም adacompliance@auroragov.org ያነጋግሩን።
0% answered
